
ለፉትቦል ማናጀር አድናቂዎች ሰበር ዜና! ስፖርትስ ኢንተራክቲቭ ፉትቦል ማናጀር በ2025 እንደማይለቀቅ እና ለ2026 መዟዟሩን በይፋ ገልጹ።
በመጀመሪያ ኖቬምበር 2024 ይለቃቃል ተብሎ ቀጠሮ ተይዞለት የነበረ ቢሆንም፣ ድጋሚ ወደ ማርች 2025 እንዲዘዋወር ተደርጎ ነበር። FM 2025 በዩኒቲ የተዘጋጀ የግራፊክስ ሞተር እና የሴቶች እግር ኳስን ያስተዋውቃል ተብሎ የሚጠበቅ ጌም የነበረ ሲሆን፣ ሆኖም ግን፣ ጌሙ በሚዘጋጅበት ወቅት ቴክኒካል እክሎች ዝግጅቱን ከባድ እንዳደረጉት እና ሙሉ በሙሉ ሳይዘጋጅ ቢለቀቅ የፍራንቻይዙን ጥሩ ስም ሊያበላሽ እንደሚችል ስፖርትስ ኢንተራክቲቮች ገልጸዋል።
ይህን ተከትሎም አንዳንድ ተጫዋቾች ስፖርትስ ኢንተራክቲቭ ለጥራት የሚሰጠውን ትኩረት ሲያደንቁ፣ ሌሎች ደግሞ ዘግይተው ማሳወቃቸውን እና ቃላቸውን መጠበቅ አለመቻላቸውን ተችተዋል።
FM 2025ን ቀድመው አዘው የነበሩ ተጫዋቾች ገንዘባቸው ሙሉ በሙሉ ተመላሽ ይደረግላቸዋል።
ስፖርትስ ኢንተራክቲቮች FM 2026 በግራፊክስ፣ በጨዋታ እና በቴክኖሎጂ ትልቅ ማሻሻያዎችን ያካተተ ታሪካዊ ጌም እንደሚሆን ቃል ገብተዋል።
ተጫዋቾች ፉትቦል ማናጀርን ረዘም ላለ ጊዜ መጠበቅ የሚኖርባቸው ቢሆንም፣ ስፖርትስ ኢንተራክቲቭ ተጫዋቾችን ለመካስ በቁርጠኝነት የተነሱ ይመስላሉ።